የዜ

Yesterday · 12 min
የሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
የሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ-ዜና በራያ አላማጣ ግንባር ወታደራዊ ፍጥጫ እና የጦርነት ዝግጅት ማየሉን ነዋሪዎች ገለጹ። በአካባቢው ፣ ቤት ለቤት ዝርፊያ መስፋፋቱን የትራንስፖርትና የባንክ አገልግሎት በመስተጓጐሉ ደንበኞች ለተጨማሪ ክፍያ መዳረጋቸውንም ተናግረዋል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ጦርነት ሸሽተው ከትግራይ ክልል ወደ ሱዳን እየገቡ ነው ሲል ኤ ኤፍ ፒ ዘገበ። ከመካከላቸው ቁስለኛ ተዋጊዎች ይገኙበታል የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚካሄደውን ጦርነት ከፍጻሜ ለማድረስ ዛሬ ሰኞ ድርድር ይጀመራል ሲሉ ቴህራን ደግሞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያካሄድኩ አይደለም ብላለች
















