Artwork for የዓለም ዜና
News

የዓለም ዜና

DW

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።

  • 100 episodes
  • Updated Monday

Episodes100

  • May 15 · 11 min

    የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና -በደቡብ አፍሪካ የመጤ ጠል እንቅስቃሴ ጋብ አያለ ቢመጣም «ሕገ ወጥ ግንባታ» በሚል ምክንያት ሱቆቻቸው እየፈረሱባቸው እንደሚገኙ ፍልሰተኛ ኢትዮጵያዊያውያን ለዶቼቬለ ተናገሩ ። -በኮንጎዋ ኢቱሪ ክፍለ ሀገር በተከሰተ አዲስ የኤቦላ ወረርሽኝ 65 ሰዎች መሞታቸውን መታወቁን የአፍሪቃ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል አስታወቀ። -የብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለሁለት ቀናት ኒው ዴልሂ ህንድ ውስጥ ያካሄዱትን ጉባኤ የጋራ መግለጫ ሳያወጡ ዛሬ አበቁ።

  • May 14 · 14 min

    የዓለም ዜና፤ ግንቦት 6 ቀን 2018 ሐሙስ

    አርስተ ዜና -የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና በፕሬዚዳንት ዢ ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸዉ። ትራምፕ አስደናቂ መሪ ሲሉ ዢ ጂንፒንግን አሞካሽተዋቸዋል። የሁለቱ ሀገራት "የተረጋጋ" ግንኙነት ለዓለም ፋይዳ እንደሚሆን የተናገሩት ዢ ጂንፒንግ በበኩላቸዉ፤ የታይዋን ጉዳይ በአግባቡ ካልተያዘ ግን ግጭት ሊፈጠር ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።-ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ በዩናይትድ ስቴትስ ከ4 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የቆየው የጦር መሣሪያ ማዕቀብ መነሳቱ ተገለፀ። ዩናይትድ ስቴትስ ኤርትራ ላይ የጣለችዉን ማእቀብ ለማንሳት እያሰበች እንደሆን ያስታወቀችዉ በዚሁ ሰሞን እንደሆን የሚታወስ ነዉ።

  • May 13 · 11 min

    የግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    ትናንት ከአሶሳ ወደ መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ ይጓዙ በነበሩ ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈጸመ የታጣቂዎች ጥቃት የበርካቶች ሕይወት አለፈ። የፈረንሳይ ፕሬዝደንት ማኑዌል ማክሮ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፈረንሳዩ መሪ ጋር በጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የሁለትዮሽ ውይይት ማካሄዳቸውን በማኅበራዊ መገናኛ ገጻቸው አመልክተዋል። ጋና ከደቡብ አፍሪቃ 300 ዜጎቿን ልታወጣ መሆኑን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ከቀትር በኋላ ቻይና ገብተዋል። የትራምፕ ጉዞ በ9 ዓመት በአሜሪካ ፕሬዝደንት ወደ ቻይና የተደረገ የመጀመሪያ ጉብኝት ነው።

  • May 12 · 10 min

    የግንቦት 4 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    -አርዕስተ ዜና -በጅቡቲ ወይም በሶማሊያ በኩል የአደን ባሕረ-ሠላጤን አቋርጠዉ ወደ አረብ ሐገራት ለመሰደድ የሚሞክሩ በርካታ ኢትዮጵያዉያን ቢሞቱም፣ ሌሎች መሰደዳቸዉን አለማቆማቸዉን ዓለም አቀፉ የፍልስተኞች ድርጅት አስታወቀ።-የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ ምሥራቅ አፍሪቃ ዉስጥ የሚደረጉ ግጭቶችን ለማስወገድ ኢትዮጵያ «ጠቃሚ» ያሉትን ሚና እየተወጣች ነዉ በማለት አደነቁ።--ፈረንሳይ ከአፍሪቃ ሐገራት ጋር ያላትን ወዳጅነት በአ,ዲስ መልክ እንደምታጠናክር አስታወቀች።ፈረንሳይ ከቀድሞ ቅኝ ግዛቶችዋ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪ የምዕራብ አፍሪቃ ሐገራት ጋር ከተቃቃረች ወዲሕ ፊቷን ወደ እንግሊዝኛ ተናጋሪዎቹ አዙራለች

  • May 11 · 12 min

    የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የፀረ ሽብር እና ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ችሎት ፣የክስ ሂደታቸው "በኘላዝማ" እንዲታይ ተወስኖባቸው የነበሩ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ሥር ያሉ የሽብር ተከሳሾች ጉዳያቸውን በአካል እንዲከታተሉ ዛሬ ብይን ሰጠ። ሱዳን ውስጥ በተፈጸሙ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮኖች) ጥቃቶች ከጥር እስከ ሚያዚያ ቢያንስ 880 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የተመድ አስታወቀ። በተመድ የአፍሪቃ ውክልና እንዲጨምር የተሀድሶ እርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉ የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶንዮ ጉተሬሽ አሳሰቡ ።

  • May 10 · 8 min

    የግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • በሰሜናዊ ምስራቋ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግዛት ኢቱሪ 69 ሰዎች በሚሊሺያዎች መገደላቸውን የአካባቢው ምንጮች እና የጸጥታ አካላት ተናገሩ። • በማዕከላዊ ማሊ በተመሳሳይ ጂሃዲስቶች አደረሱ በተባለ መጠነ, ሰፊ ጥቃት በ,ርካታ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው የጸጥታ ምንጮች ትናንት ቅዳሜ አስታወቁ። • ኢራን አሜሪካ ላቀረበችላት የሰላም ስምምነት መልስ መስጠቷን የሀገር ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ዘገቡ ። • ሩስያ በዩክሬን የምታደርገው ጦርነት በፍጥነት እንዲያበቃ ፍላጎት እንዳላት አስታወቀች። • በሃንታ ቫይረስ በተመታች የመዝናኛ መርከብ ላይ ያሉ ተጓዦችን የማስወጣት ስራ በይፋ ተጀመረ።

  • May 9 · 11 min

    የቅዳሜ ግንቦት 1 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    በዛሬው የዓለም ዜና በአዲስ አበባ ሽሮ ሜዳ አከባቢ ባለፈው ሓሙስ «በአንድ የፖሊስ አባል የተገደለ» ወጣት ትናንት ዓርብ ስርዓተ ቀብሩ መፈጸሙን ፤የናይጄሪያ ጦር በሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል 50 ፅንፈኛ ያላቸውን ታጣቂዎች መግደሉን ማስታወቁን፤የዓለም ጤና ድርጅት ሀላፊ የሃንታ ቫይረስ የተከሰተበት መርከብ ከመድረሱ በፊት ስፔን መግባታቸው መገለፁን፤ ሂዝቦላህ በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ የእስራኤል ወታደሮች ላይ ያነጣጠረ የድሮን ጥቃት ማድረጉን መግለፁ፣ሞስኮ በጠንካራ ጥበቃ ስር ዛሬ የድል ቀን በዓልን ማክበሯን፣ኢራን በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እንደምትሳተፍ ማስታወቋን አካቷል።

  • May 8 · 10 min

    የዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    መቐለ፥ሕወሓት ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ ከመረጠ በኋላ ዛሬበይፋ ሥራ መጀመሩን ዐሳወቀ፤ ናይሮቢ፥ የፈረንሣይ ፕሬዚደንት ሦስት የአፍሪቃ አገራትን ሊጎበኙ ነው፤ ሞቃዲሾ፥ ሶማሊያ ውስጥ ብርቱ የረሐብ አደጋ እልቂት እንዳይፈጥር አስግቷል፤ ሪያድ፥ በኢራን ፍኖተ-ሆርሙዝ ዘመቻዋ ዩናይትድ ስቴትስ የዓየር ክልሏን እንዳትጠቀም ሣዑዲ ዓረቢያ አገደች፤ ቴህራን፥ ኢራን መርከቦቼ ላይ ጥቃት አደረሰችብን ያለቻት ዩናይትድ ስቴትስን አስጠነቀቀች፤ ዋሽንግተን፥ ዩናይትድ ስቴትስ የኢራን መርከቦች ላይ ተኩስ ከፈተች

  • May 7 · 10 min

    የሐሙስ ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የሐሙስ ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና -ደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ አፍሪቃዉያን ስደተኞች ላይ የሚፈፀመው ጥቃት ተባብሶ መቀጠሉ ይበልጥ እንዳሰጋቸው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለዶቼቬለ ተናገሩ። -የናፍጣ እጥረት ባናረው የጭነት መጓጋዣ ዋጋ ምክንያት፣ የሙዝ ምርታቸውን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መቸገራቸውንና ለኪሳራ እየተዳረጉ መሆኑንም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋሞ ዞን ሙዝ አምራች አርሶ አደሮች ዐሳወቁ። -ዩናይትድ ስቴትስ በቅርቡ የኢራኑን ጦርነት ለማስቆም ያቀረበችውን የሰላም እቅድ እየገመገመች መሆኑን ኢራን አሳወቀች።

  • May 6 · 9 min

    ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በሱዳን አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን ጥቃት) እጄ የለበትም ስትል አስተባበለች ። • የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በቻድ ሐይቅ ዳርቻ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ ባደረሱት ጥቃት በትንሹ 23 ወታደሮች ተገደሉ ፤ ሌሎች 26 ቆሰሉ ። • አሜሪካ እና ኢራን የባሕረ ሰላጤውን ጦርነት ለማቆም ከስምምነት ለመድረስ መቃረባቸው ተሰማ። • በገዳዩ የሀንታ ተሐዋሲ የተጠረጠሩ ሦስት ተጓዦች ከመንገደኞች መርከብ ተለይተው ወደ ኔዘርላንድስ መወሰዳቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።

  • May 5 · 10 min

    የማክሰኞ ሚያዝያ 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    መቀለ፥ ሕወሓት ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤልን የትግራይ ክልል ፕረዚደንት አድርጎ መረጠ፤ ናይሮቢ፥ ኢትዮጵያና ሱዳን አንዱ ሌላኛውን በማጥቃት እየተካሰሱ ነው፤ አስመራ፥ ዩናይትድ ስቴትስ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማእቀብ ልታነሳ ነው መባሉ፤ ዋሽንግተን፥ ዩናይትድ ስቴትስ በሆርሙዝ ሠርጥ መርከቦችን ብታስተናብርም የተኩስ አቁሙ ግን እንደተጠበቀ ነው አለች፤ ዬርቬና፥ የአውሮጳ ኅብረት የትራምፕ የቀረጥ ዛቻ ለሚያስከትለው ማንኛውም ነገር ዝግጁ መሆኑን ዐሳወቀ፤ ለንደን፥ ዩክሬንን ለማጥቃት ለሩስያ ተዋጊዎችን የሚመለምሉ ላይ ብሪታንያ ማእቀብ ጣለች፤ ላይፕትሲሽ፥ በተሽከርካሪ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ ፍርድ ቤት ሊቀርብ ነው

  • May 4 · 11 min

    የዓለም ዜና፤ ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ሰኞ

    አርስተ ዜና--የጀርመን መራሄ መንግሥት ፍሬድሪክ መርስ ፤ ዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ 5,000 የአሜሪካ ወታደሮች ከጀርመን ጦር ሰፈር ለማዉጣት ማቀዳቸዉ የሚያስደንቅ እንዳልሆነ ተናገሩ። ኔቶ በበኩሉ አውሮጳውያን፤ የአሜሪካኑን ፕሬዝዳንት የብስጭት መልእክትን «ሰምተው» ቁርጠኝነታቸዉን እያጠናከሩ ነዉ ሲል መልስ ሰጥቷል።-የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (ኢሶዴፓ) ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያቀረባቸውን 309 ዕጩዎች ከውድድሩ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ። -በእስር ላይ የሚገኙ ከአርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን ጋር ቅርበት ያላቸው ሰባት ሰዎች መካከል እስካሁን ፍርድ ቤት በቀረቡት ሁለቱ ላይ ፖሊስ የ14 ቀን ቀጠሮ ጠይቋል።

  • May 3 · 8 min

    የሚያዚያ 25 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

    • የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በመዲናዪቱ ካርቱም (RSF) ተፈጸመ በተባለ የድሮን ጥቃት አምስት ንጹሐን ዜጎች መገደላቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች አስታወቁ። • በኤደን ባሕረ ሰላጤ ላይ ሌላ የነዳጅ መርከብ በባሕር ላይ ወንበዴዎች ተጠለፈች • ኢራን በ30 ቀናት ውስጥ ግጭቱ እንዲቆምና የአሜሪካ ማዕቀቦች እንዲነሱ የሚጠይቅ የ14 ነጥብ የሰላም ዕቅድ አቀረበች። • ኢትዮጵያዊው አትሌት ብርሃኑ ወንድሙ ዛሬ የተካሄደውን 31ኛው የፕራግ ዓለም አቀፍ ማራቶን አሸነፈ።

  • May 2 · 9 min

    የሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    በኬንያ ሰሞኑን በጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፋና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 10 ሰዎች ሞቱ። ታይዋን ፕሬዝዳንት ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ዲፕሎማሲያዊ አጋር ሀገር ኤስዋቲኒ ገቡ።3,000 የሚጠጉ የየመን ስደተኞች ከዩናይትድ ስቴትስ እንዳይባረሩ አንድ የፌዴራል ዳኛ ከለከሉ። የነዳጅ ዘይት የጫነ አንድ መርከብ ከየመን የባህር ዳርቻ ተጠለፈ። ዩናይትድ ስቴትስ 5000 የሚጠጉ ወታደሮቿን ከጀርመን ልታስወጣ ነው። የአውሮፓ ህብረት እና የጀርመን ኢንዱስትሪዎች የትራምፕን አዲስ የታሪፍ ዕቅዶች ተቹ።የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ክልሉ ሙሉ በሙሉ ለመደበኛ በረራዎች ክፍት እንደሚሆን አስታወቁ።

  • May 1 · 11 min

    የሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    የአውሮጳ ሕብረት ትግራይ ክልል ውስጥ ሌላ አውዳሚ ጦርነት ከሚያስከትል እርምጃ ሁሉም ወገኖች እንዲታቀቡ አሳሰበ። ኢትዮጵያዊን ጨምሮ ዘጠኝ አፍሪቃውያን ስደተኞችን የአሜሪካ መንግሥት ወደ ካሜሮን ማባረሩን ጠበቃቸው ተናገሩ። የተመድ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ኢቱሪ ክፍለ ሀገር ጁጉ ግዛት በደረሰ ጥቃት ምክንያት ወደ 200 ገደማ ነዋሪዎች ተፈናቅለው መጠለያ እንደሚያስፈልጋቸው አመለከተ። የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ደቡብ ሱዳን ውስጥ ያሰማራውን የሰላም አስከባሪ ኃይል ቁጥር ለመቀነስ ወሰነ። የሰላም አስከባሪውን የቆይታ ጊዜም እስከ መጪው ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2027 ሚያዝያ 30 ቀን ድረስ አራዝሟል።

  • April 30 · 9 min

    የዕለተ ሐሙስ ሚያዝያ 22 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    መስቃን፥ በምሥራቅ ጉራጌ ዞን አምስት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ፤ ናይሮቢ፥ በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊውን ለጥቂት ቀድሞ ክብረወሰን ያስመዘገበው ኬኒያዊው አትሌት የጀግና አቀባበል ተደረገለት፤ ብራስልስ፥ በዩናይትድ ስቴትስ እና ሩስያ ፕሬዚደንቶች መካከል የተደረገው የስልክክ ንግግር አውሮጳን ግራ አጋብቷል፤ ቴሕራን፥ የአሜሪካ የፍኖተ ሆርሙዝ የመርከቦች ፍሰት ክልከላ በአካባቢው አደገኛ አለመረጋጋት ይፈጥራል አለች፤ ቤርሊን፥ የኢራን ጦርነት ዓለምን ቢያስጨንቅም ጀርመን ያልተጠበቀ የኤኮኖሚ እድገት ዐሳይታለች፤ ለንደን፥ ብሪታንያ አይሁዶችን ከጥቃት ለመከላከል ተጨማሪ 25 ሚሊዮን ፓውንድ ለመመደብ ቃል ገባች

  • April 29 · 11 min

    የሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

    ሳውድ አረቢያ ውስጥ ቢያንስ 65 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተገናኘ ወንጀል የሞት ቅጣት እንደሚያሰጋቸው ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተቋም ሂውማን ራይትስ ዎች ዐሳወቀ። ለሁለት ሳምንታት የደረሰበት ያልታወቀው የአዲስ ስታንዳርድ አርታኢ ሚሊዮን በየነ ትናንት ወደ ቤቱ መመለሱን አሠሪው ድርጅት ገለጸ። የዩጋንዳ ባለሥልጣናት ከሕገወጥ የሰዎች ሽግግር እና በበይነ መረብ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በርካታ የውጭ ዜጎች ማሰራቸውን አስታወቁ። ሥር ለሰደደ የምግብ እጥረት የተጋለጠችው ሶማሊያ በማያባራው ግጭት እና የገንዘብ እጥረት ምክንያት ከፍተኛ የሰብአዊ እርዳታ እንደሚያስፈልጋት የተመድ አመለከተ።

  • April 28 · 12 min

    የሚያዝያ 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና

    በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን፣ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ20 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በ62 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ተገለጸ። በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ሦስት ኢትዮጵያዊያን በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን ታውቋል። ኢትዮጵያዊያኑ ትናንት የተገደሉት በአንድ ምግቤት ውስጥ በመመገብ ላይ እንዳሉ ነው ፡፡ባሕሬይን አስፈላጊ ተቋሞቿን ፎቶ በማንሳት ለኢራን አስተላልፏል ያለቻቸውን 5 ሰዎች የዕድሜ ይፍታህ እስር ውሳኔ አስተላለፈች። አሜሪካ፤ ኢራን ያቀረበችው የመደራደሪያ ሐሳብ እያጤነችው መሆኗን አስታወቀች።

  • April 27 · 11 min

    የሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉና በልዩ ሁኔታ የሚመዘገቡ መራጮች ምዝገባ ማከናወን ዛሬ መጀመሩ አስታወቀ። በደቡብ ሱዳን አንድ አውሮፕላን ተከስክሶ በውስጡ የነበሩ 14 ተሳፋሪዎችና የበረራ ሰራተኞች በሙሉ አለቁ። የሶማሊያ የባሕር ወንበዴዎች በሶማሊያ የባሕር ክልል ስትጓዝ የነበረችው ስሚንቶ የጫነች መርከብ አገቱ። ሒዝቦላህ፤ ሊባኖስ ከእስራኤል ጋር የምታካሂደውን ቀጥታዊ ውይይት ውድቅ አደረገ።የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሐገራቸው የኢራንና በቀጠናው ያሉ ሐገራትን ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች» አሉ።

  • April 26 · 9 min

    የሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

    የማሊ የመከላከያ ሚኒስትር ሳዲዮ ካማራ በጂሃዲስቶች ጥቃት ተገደሉ። በማዕከላዊ አፍሪቃዊቷ ሀገር ቻድ ሰላማዊ ሰልፍ የጠሩ ዘጠኝ የተቃዋሚ ንቅናቄ ቡድን ኃላፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተገኙበት የእራት ግብዣ ስነ ሥርዓት ላይ ተኩስ መከፈቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ በርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች ዛሬ ድርጊቱን ኮንነዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ዛሬ እሁድ ዩናይትድ ስቴትስን እና ኢራንን ወደ ምታደራድረው ፓኪስታን መዲና ኢስላማባድ ተመለሱ። ኬንያዊው ሴባስቲያን ሳዌ በማራቶን ታሪክ ከሁለት ሰዓት በታች የሮጠ የመጀመሪያው አትሌት ሆነ።