Artwork for ዜና መጽሔት
News

ዜና መጽሔት

DW

በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።

  • 100 episodes
  • Updated Yesterday

Episodes100

  • Yesterday · 18 min

    የሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    የዜና መጽሔት ዝግጅታችን ሰሞነኛው የግጭት መረጃ እና የመገናኛ ብዙኃን የይዘት አቀራረብ አንደምታ፤ በትግራይ ድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰው ጦርነት በርካቶች ወደ ሱዳን እንዲሰደዱ ማስገደዱ፤ በቆቦ አካባቢ ወታደራዊ ዝግጅት መጠናከሩ እንዲሁም ሕይወት የቀጠፈ የመሬት መንሸራተት አደጋ በጻድቃኔማርያም ገዳም መከሰቱን የሚመለከቱ ዘገባዎችን አካቷል

  • Friday · 27 min

    የሐምሌ 24 ቀን 2018 የዜና መጽሔት

    አንድ የጀርመን ተቋም በኢትዮጵያ ግጭት እንዳይከሰት የሰጠው ምክረ-ሐሳብ፤ ፌደራል ፖሊስ በደቡብ ኢትዮጵያ መስመር በሕገወጥ ሰዎችን የሚያሸጋግሩትን መቆጣጠሩን መግለጹ፤ የተማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን ኢላማ ያደረገው የኢንተርኔት ማጭበርበር፤ ዋግህምራ ዞን አበርገሌ እና ጻግብጂን የተቆጣጠረዉ ታጣቂ ቡድን ተዋጊዎችን እየመለመለ ነው መባሉ፣ መተከል ዞን ከጉባ-ግልገል በለስ የተበላሸው መንገድ፤ እንዲሄም ሮም ጣሊያን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው በአውሮጳ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ድግስን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።

  • Thursday · 26 min

    የሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት

    1, የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመረጃ ተደራሽነት ላይ የተሰጡ አስተያየቶች 2, የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤና የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ 3, በትግራይ የተመናመነው ሰብዓዊ ድጋፍ እና የተፈናቃዮች እሮሮ 4, የአዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ በድሬደዋ 5, ጣና ሐይቅን እየፈተነ ያለዉ የእምቦጭ አረም //እንዲሁም 6, አፍሪካ ኀብረት በሶማሊያ ያለው ሚና ወደ ፖለቲከዊ ተልዕኮ እንዲሸጋገር መጠየቁ

  • Wednesday · 20 min

    የሐምሌ 22 ቀን 2018 የዜና መጽሔት

    በዜና መጽኄት አምስት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ግድያና ጥቃትን የተመለከቱ የምርመራ ውጤቶች ትኩረት አግኝተዋልን? ሲል የሚጠይቀው ቀዳሚው ዘገባችን ነው ። ከ90 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በ4 ጣቢያዎች ለብርቱ ዝናምና ጎርፍ ተጋልጠዋል መባሉ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዓመቱ ስኬቶች እና ያጋጠሙት ፈተናዎች፤ IOM ምስራቅ አፍሪቃውያን በዓለም አቀፍ ወንጀል እንዲሳተፉ እየተገደዱ ነው ማለቱ እንዲሁም የሰው ሠራሽ አደጋ በማጃንግ ዞን ጥብቅ ደን ላይ አደጋ ደቅኗል ይሰኛሉ ዘገባዎቹ

  • July 28 · 22 min

    የዜና መጽሔት፤ ሐምሌ 21 ቀን 2028 ዓ.ም ማክሰኞ

    የዜና መጽሔት ጥንቅራችን ዩናይትድ ስቴትስና ኢትዮጵያ በጋራ ያዘጋጁትን ሲምፖዚየም አላማ ፤ትግራይ ክልል ለ2019 በጀት ዓመት 65 ቢሊዮን ብር ማፅደቁ ከመቀሌ ሲነገር፣ በክልሉ ይደረጋል ያሉትን ወታደራዊ ምልመላና ጦርነት ያሰጋቸዉ ወጣቶች በብዛት መሸሻቸዉ ከአማራ ክልል ተዘግቧል።የደቡብ ኢትዮጵያ አስተዳደር በአደጋ ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች ቤት መስራቱ እንዲሁም የአፍሪቃ ሕብረት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮችን ስብሰባ በአዲስ አበባ የተሰኙ ዘገባዎችን አካቷል።

  • July 27 · 18 min

    የሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሄት

    የዛሬው የዜና መ።ፅሄት፤ ለአማራ እና ለትግራይ ምኁራን የቀረቡ የትብብር ጥሪዎችና ያላስማሙ ተቃርኖዎች፣በምስራቅ ወለጋ ዞን በታጣቂዎች የደረሰው ጥቃት፣የደቡብ አፍሪቃዉ መጤ ጠል ጥቃትሃገሪቱን ከአፍሪቃ ማቃረኑ እንዲሁም የኢትዮጵያ የፊልም ፌስቲቫል በፓሪስ የተሰኙ ርዕሶችን ያስተነትናል።

  • July 24 · 25 min

    የዕለተ ዐርብ ሐምሌ 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    የዓለም ዜናን የሚከተለዉ የዜና መጽሔት፤ -በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ነው ያለው የዘር ማጥፋት እና የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቆም፣ ሲል ጥሪ ያቀረበዉ የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ -በትግራይ ክልል እየተደረጉ ያሉ ሰሞነኛ ስብሰባዎችና የነዋሪዎች ኹኔታ - በቀይ ባሕር በሁቲ ታጣቂዎች የተፈፀ የመርከቦች ጥቃትን የአፍሪካ ኅብረት ማዉገዙ -የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎትን ለማስተሳሰር ያለመ አዲስ ፍኖተ-ካርታ ይፋ መሆኑ - እንዲሁም ተግባራዊ የሆነው ተንቀሳቃሽ ማህበረሰብ አቀፍ የጤና ፕሮግራም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሰኙ ርዕሶችን ይዟል።

  • July 23 · 24 min

    የሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    በዜና መጽኄት አምስት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ዘገባዎቹ፦ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን፦ የምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች በሚያቀርቡት ሐሳብ እንዳይጠየቁ ኃላፊነት እወስዳለሁ ማለቱ፤ የድሮን ጥቃት በአባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም፣ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነሰ) ከሌሎች ታጣቂዎች ጋር ስለመተባበር ምን አለ? ደቡብ አፍሪቃ፡ ኢትዮጵያውያን በፈቃደኝነት ወደ አገራቸው የተመለሱ ነዉ፤ እንዲሁም የአሜሪካ ሕግ አውጪ ምክር ቤት ስለ ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት፤ ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ።

  • July 22 · 18 min

    የሐምሌ 15 ቀን 2018 የዜና መፅሔት

    ዜና መፅሔቱ፣ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሲቪል ማሕበራት ተሳትፎ እና የታዛቢነት ሚና፣ ደብረብርሀን መጠለያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች ሮሮ ፣ የግብፅ የህዳሴ ግድብ ውንጀላና የኢትዮጵያዊው ተደራዳሪ ምላሽ፣ እንዲሁም በትግራይ የሰላሙ ተስፋ ምን ይመስላል? በተሰኙ ርዕሶች ስር የተቀናበሩ ዘገባዎች ይቀርቡበታል

  • July 20 · 19 min

    የሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    የዜና መጽሔት ዝግጅታችን ፣ የኦሮምያ ክልል ምክር ቤት ጨፌ ስለክልሉ የፀጥታው ሁኔታ መምከሩን፣ -በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በአዲስ ጉባኤዉን የተቀላቀሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሉ መባሉን፣ -በደቡብና ሰሜን ወሎ በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸም ዝርፍያ መባባሱ፣ -የአፍሪቃ ቀንድን የበለጠ ስጋት ዉስጥ የጣለዉ የአሜሪካ እና የኢራን ዳግም ግጭት የተሰኙ ርዕሶችን በስፋት ይዳስሳል

  • July 17 · 25 min

    የሐምሌ 10 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    የዓለም ዜናን የሚከተለዉ የምሽቱ የዜና መጽሔት፤ በአማራ ክልል በሴቶች ላይየሚደርሰው ወሲባዊ አካላዊና ጥቃት ተባብሷል መባሉ፤ በጊምቢ ወደ ቀያቸው የተመለሱ ዜጎች ቅሬታ፣በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር የሰሜን ኢትዮጵያ ጉብኝቶች፣በትግራይ የሰላምና ለውጥ ም/ቤት በአዲስ አበባ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እንዲሁም በአሜሪካ ምርጫ ቻይና ጣልቃ ገብታለች ሲሉ ቻይናን የከሰሱት ዶናልድ ትራምፕ የተሰኙ ርዕሶችን በስፋት ይዳስሳል።

  • July 16 · 27 min

    የሐሙስ ሐምሌ 9 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት፦ ትናንት ስለተጀመረው የኢትዮጲያ ብሔራዊ የምክክር ጉባኤ የተሳታፊዎች አስተያየት ፣ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው መጀመር፣ አካሄድ እና ውጤቱ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስተያየት በምክክሩ የሚሳተፉ ተወካዮቻቸውን የላኩት ተፈናቃዮች ከጉባኤው የሚጠብቁት፤ እንዲሁም የኢትዮጵያ የወደብና የቀይ ባህር ወሰን ጥያቄ ፣ አሜሪካ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በተመለከተ የወሰደችው የፖሊሲ ለውጥ የዓለም እግር ኳስ የግማሽ ፍጻሜና የፍጻሜ ጨዋታዎች የዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያስቃኘን ጉዳዮች ናቸው።

  • July 15 · 20 min

    የሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    የዜና መጽሔት ቀዳሚው ዘገባ ዛሬ በይፋ የተጀመረውን ብሔራዊ ምክክር ጉባኤ ይመለከታል፤ የአየር ንብረት መዛባት በክረምቱ ግብርና ላይ የደቀነው ስጋት፤ የአሜሪካው አምባሳደር የመቀለ ጉብኝት፤ አሜሪካ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በተመለከተ የወሰደችው የፖሊሲ ለውጥ እንዲሁም የትናንቱን የፈረንሳይ ስፔን ጨዋታ እና የዛሬውን የዓለም ዋንጫ ተጋጣሚዎች የሚመለከቱ ዘገባዎችን አካቷል

  • July 14 · 30 min

    የዜና መጽሔት፤ ሐምሌ 7 ቀን 2028 ዓ.ም ማክሰኞ

    በዜና መጽኄት ስድስት ዘገባዎችን ይዟል- የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜን በተለመለከተ ቃለ መጠይቅ ነው ። ነገ ስለሚጀመረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሰዎች ምን ይላሉ?፣ ነገ ስለ ሚጀረው የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ምን ተባለ?፣ በአማራ ክልል የተፈናቃዮች የድረሱልን ጥሪ፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አገራዊ ውይይት በጅግጅጋ እንዲሁም የጊምቢ- ኖሌካባ እና ሜቱ መንገድ ግንባታ መጓተት የሚሉ ዘገባዎችን ያስተነትናል።

  • July 10 · 28 min

    የሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    የዓለም ዜናን በሚከተለው በዛሬው የዜና መጽሄት ፣ በእሥር ላይ ስለሚገኙ ፖለቲከኞች መፈታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሰጡት ፍንጭ፤ በአርሲ አሰኮ በግጭት የተፈናቀሉ ነዋሪዎች የድጋፍ ጥያቄ፤ የኢሰመኮ የአምስት ዓመት ዕቅድ የመብት ጥሰቶችን ይቀንስ ይሆን?፤ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ወቀሳ የህወሓት ምላሽ፣ በአፍሪቃ የሚካሄዱ ምርጫዎች ዳያስፖራውን ማሳተፍ እንደለባቸው መገለጹ እንዲሁም አንድነት ላይ ያተኮረው የኔቶ ጉባኤ ይሰኛሉ ዘገባዎቹ ። የወጣቶች ዓለም መሰናዶ ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች፦ የመረጃ ሰጪ መተግበሪያዎች የንባብ ባህልን እያዳከሙ ይሆን? በሚል ርእስ ተቀናብሯል ።

  • July 7 · 20 min

    የማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    የዜና መጽሔት ጥንቅራችን፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ለጦርነት እየተዘጋጀ ነዉ ሲሉ፣ -የዚያዉ ከትግራይ ክልል ወጣቶች ደግሞ አፈሳና የጦርነት ዝግጅት እንዳሳሰባቸዉ እያስታወቁ ነዉ።የዳግም ጦርነት ዝግጅት፣ ወቀሳና ሥጋቱን ዜና መጽሔቱ በሁለት ዘገቦች ያስተነትናል።የኢትዮጵያ ምርጫ የጥቃት ኢላማ እንደነበር፣ የሐገሪቱ ምጣኔ ሐብት ግን ዘንድሮም በ10.2 በመቶ አድጓል መባሉ ከወደ አዲስ አበባ ተሰምቷል።ሌላዉ የዜና መፅሔት ርዕስችን በሱዳንዋ ሥልታዊ ከተማ አል-ዑቤይድ የተፈፀመዉ የመብት ጥሰትና ይደርሳል የተባለዉ ተጨማሪ ጥፋት የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ኮሚሽንን እያባተለ መሆኑን ይቃኛል።