Artwork for ዜና መጽሔት
News

ዜና መጽሔት

DW

በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።

  • 100 episodes
  • Updated Yesterday

Episodes100

  • April 15 · 19 min

    የሚያዝያ 7 ቀን 2018 የዜና ፅሔት

    በዜና መጽኄት አራት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ኢሕአፓ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በሚመለከት ለምርጫ ቦርድ ደብዳቤ መጻፉን ገለፀ፤ ደቡብ ወሎ ዞን ፓስፖርት ለማውጣት 161 ሐሰተኛ ሰነዶች፤ የኢራኑ ጦርነት፣ ለሱዳኑ ግጭት የሚሰጠው ትኩረት እንዲቀንስ ማድረጉ ተገለፀ እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ የመርከቦች እገዳ በፍኖተ ሆርሙዝ ለኢራን ምን አመጣ? ይሰኛሉ ዘገባዎቹ፣

  • April 14 · 22 min

    የሚያዚያ 6 ቀን 2018፤ የዜና መፅሄት

    ዜናውን ተከትሎ በሚቀርበው የዛሬ የዜና መፅሔታችን ፤መራጮች ምን ይላሉ?፣በነጻ የንግድ ቀጠና ባለሃብቶችን ከገቢ ግብር ነጻ የሚያደርገው መመሪያ፣በአማራ ክል ተፈናቃዮች የምግብ ዕርዳታ ከተሰጠን 2 ወራት አለፉ ማለታቸውን ፣እንዲሁም የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስሱ ጥንቅሮች አካቷል። ሳምንታዊዎቹ ጤና እና አካባቢ እና አውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅቶችም ተካተዋል።

  • April 13 · 19 min

    የመጋቢት 5 ቀን 2018 የዜና መፅሔት

    ዜና መጽሔት ጥንቅሩ፤ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት እና በሂደት የሚያስከትለው ጫና፤2, በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮንሶ ዞን ነዋሪዎችን እየፈተነ ያለዉ የኤሌክትሪክ መቋረጥ፤ በተለያዩ የዓማር ክልል ከተሞች የንግድ ማህበረሰቡን የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እንዲሁም ባለፈዉ ሰሞን በባሌ ሮቤ መናኸሪያ ላይ በወጣት ወንጀለኞች ተደበደቡት አባት የተሰኙ ርዕሶችን አካቷል።

  • April 10 · 23 min

    DW Amharic የሚያዝያ 02 ቀን 2018 ዜና መጽሔት

    የነዳጅ እጥረት፣ የመጓጓዣ ዋጋ እና የጤፍ አቅርቦት፤ የመሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች ዋጋ መጨመር፤ ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ሕብረት የሠላምና ፀጥታ ምክር ቤት የአንድ ወር ሊቀመንበር ሆነች፤ የእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ተኩስ አቁም ያሳደረዉ ተስፋ በኢትዮጵያ፤ የአሜሪካና ኢራን ጦርነት የተኩስ አቁም ስምምነት

  • April 8 · 32 min

    የመጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ ም ዜና መጽሔት

    የዜና መፅሔት ዝግጅታችን፣የትግራይ ክልል ጊዚያዊ ፕሬዝደንት የጄኔራል ታደሰ ወረደ ዘመነ-ሥልጣን ለተጨማሪ አንድ ዓመት መራዘሙንና ያስከተለዉን ቅሬታ የሚቃኘዉን ዘገባ ያስቀድማል።በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞንን የመታዉ ድርቅ ከሁለት ወረዳ ብቻ ከ4000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸዉ ተሰምቷል።የአፍሪቃ ሕብረትና የኢትዮጵያ መሪዎች በአንጋፋዋ ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ሞት የተሰማቸዉን ሐዘን እየገለፁ ነዉ። ዜና መፅሔቱ ዩናይትድ ስቴትስ፣ እስራኤልና ኢራን ለሁለት ሳምንት ተኩስ ማቆማቸዉን፣ ምክንያቱንና የወደፊቱን ሁኔታ በተመለከተ ከባልደረቦቻችን ጋር የቀጥታ ዉይይት ይሰማበታልም።

  • April 7 · 17 min

    የመጋቢት 29 ቀን 2018 የዜና መጽሔት

    በዜና መጽኄት አራት ዘገባዎችን እናስተነትናለን ። ዘገባዎቹ፦ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል?፤ በነዳጅ እጥረቱ የተስተጓጎለው ትራንስፖርትና መጪው የበዓል ሸመታ፤ የነዳጅ እጥረት በአማራ ክልል የፍትህ ስርዓት ላይ እንቅፋት እየሆነ ነው መባሉ ይሰኛሉ ። እንዲሁም የዪናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን የሰጡት ቀነ ገደብ ሊጠናቀቅ ጫፍ መድረሱ እና ያጠላው ሥጋት የሚዳስስ ቃለ መጠይቅ ይኖረናል

  • April 6 · 17 min

    የመጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    በዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባን ማራዘሙ በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በማዳበሪያ አቅርቦት ላይ የፈጥረው ተፅዕኖ የለም መባሉ በአረብ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እሳት እየለበለባቸው የሚያገኙትን ገንዘብ እንዲያጠራቅሙላቸው ወደ አገር ቤት ሲልኩ መከዳታቸው የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሆርሙዝ የባሕር በር ለመክፈት ስምምነት ላይ እንድትደርስ የሰጡት ቀነ ገደብ ነገ ያልቃል በዚህና ተያያዥ ጉዳዮች ከዋሽንግተን ዲሲ ወኪላችን አጭር ቆይታ ይኖረናል።

  • April 3 · 22 min

    የመጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ፤የዜና መፅሄት

    በዛሬው የዜና መፅሔታችን በጅቡቲ መኪኖቻቸው ያለስራ የቆሙባቸው የነዳጅ ጫኝ ቦቴ አሽከርካሪዎች ምሬት፤የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ፤ኢትዮጵያ አሳካሁ ያለችው የ13 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት አንድምታ፤እንዲሁም አዲሱ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ተካተዋል።

  • April 2 · 25 min

    የመጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    የስደተኞች ሰቆቃ በየመን እና በሳውዲ አረቢያ ድንበር ላይ በትግራይ ክልል እና ውዝግብ ባለባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባ ምን ይመስላል? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያን መምራት የጀመሩበት ስምንተኛ ዓመት የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የአፍሪካ አገራትን ገንዘብ ማዳከም ጀምሯል ዶናልድ ትራምፕ ስለ ኢራን ጦርነት ለህዝባቸው ያስተላለፉት መልዕክት

  • April 1 · 19 min

    የመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    በዜና መጽሔት ዝግጅታችን አዲስ አበባ ውስጥ የተሰየመው የትግራይ ምክክር እና አንድምታው፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዲሱ “የህገወጥ ቤቶች ግንባታ” ደንብ እና ያስተናገደው አስተያየት ፤ገቢና ወጪ ሸቀጦችን የሚያጓጉዙ ከባድ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ እጥረት ሥራቸው በምን ኹኔታ ላይ ይገኛል? የሚለውን ጨምሮ ፤ በነዳጅ እጥረት ቀውስ በሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ላይ ያሳደረው ተጽዕኖን የተመለከቱ ዘገባዎች በዝርዝር የሚቀርቡ ርዕሰ ጉዳዮቻችን ናቸው ።

  • March 31 · 22 min

    DW Amharic የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዜና መጽሔት

    የኢራኑ ጦርነት የኢትዮ-ኤርትራን ውጥረት ያባብሰዋል ብለው እንደማያምኑ ተንታኞች ተናገሩ፤ እስካሁን የተቋረጠ የአገር ውስጥም ሆነ ዓለማቀፍ በረራ አለመኖሩንም ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ የቅድስት ክፍሌ መታሰቢያ የመንገድ ደሕንነት ትምሕርት፤ የነዳጅ ዕጥረት እያስከተለው ያለው ጫና፤ የኢራን ጦርነት በአውሮፓ ሐገራት ያሳደረው ጫና

  • March 30 · 19 min

    የመጋቢት 21 ቀን 2018 የዜና መፅሔት

    የዜና መጽሔት አራት ርዕሰ ጉዳዮች ይተነተናሉ እነርሱም በኦሮሚያ ክልል የተኩስ ድምጽ እንዲቆም የቀረበው ጥሪ ፣ በደቡብ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት የወልቂጤ ቅርንጫፍ FM 89.2 ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ ፣ በትግራይ ክልል ሀገራዊ ኹነቶችን ለማከናወን ያለው ወቅታዊ ኹኔታ እንዲሁም የሁቲዎች ጥቃትና ማስጠንቀቂያ በአፍሪካ ቀንድ ስጋት እንዲጨምር ማድረጉ የሚሉት ናቸው። ማኅደረ ዜና ለዛሬ ትኩረቱን የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ በኢትዮጵያ ያስከተለውን ችግር ላይ አድርጓል።

  • March 27 · 18 min

    የመጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዜና መጽሔት

    በዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ሀገራዊ የውይይት ኮሚሽን የትግራይ ክልልልን አጀንዳ ልየታ በአዲስ አበባ፤ የነዳጅ እጥረት በአዲስ አበባ እያስከተለ ያለውን ችግር የጋምቤላ ክልላዊ መንግስት ከ300 በላይ የፖሊስ መኮንኖችን ከስራ ማባረሩን እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍሪቃ የባሪያ ንግድ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ መቀበላቸው የሚቃኙ አራት ዘገባዎች ይቀርባሉ።

  • March 26 · 24 min

    የመጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሔት

    የዜና መፅሔታች በአማራ ክልል ድንገተኛ በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ያደረሰው ጥፋት፤ በርዳታ አቅርቦቱ እጥረት ተፈትነናል ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፤ በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ስላሉበት ኹኔታ ምን ይላሉ?፤ የአውሮጳ ኅብረትና የጋና የደህንነትና መከላከያ ትብብር የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮችን አካቷል።

  • March 25 · 18 min

    የረቡዕ መጋቢት 16 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    የዓለም ዜናን ተከትሎ፤ "ከምርጭ ራሳችንን እስከማግለል ርምጃ ልንወስድ እንችላለን" ሲል የ4 ፓርቲዎች ጥንር የሆነው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ መግለፁን፤ስለምርጫው የታጣቂዎች ማስጠንቀቂያ እና የፓርቲዎች አቋም የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በዛሬው ዕለት አዲስ የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባሕር ልዩ መልዕክተኛ መሾሙን እንዲሁም የአሜሪካ እና የኢራን የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን የሚቃኙ አራት ዘገባዎች ይኖሩናል።

  • March 24 · 18 min

    የመጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የዜና መፅሔት

    ዜና መጽሔት ጥንቅራችን አራት ዘገባዎች ይኖሩናል። እነሱም፤* በሱዳኗ ኩርሙክ የተከሰተው ግጭት የድንበር ነዋሪዎች ላይ የፈጠረው ስጋት፤* የሶማሌ ክልል የክልሉን ከፍተኛ ባለስልጣናትን ስም በሀሰተኛ መረጃ ለማጠልሸት እየተካሄደ ነው ያለውን ድርጊት መኮነኑ፤* የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ዮሐንስ ብርሃነ በአስቸኳይ እንዲፈታ ስለ መጠየቁ እና* በሰሜን ሸዋ ዞን ሰላሌ፤ በጠለፋ ምክንያት ለአስከፊ ጉዳት የተዳረገች የ7ኛ ክፍል ተማሪ ጉዳይ ናቸው።

  • March 23 · 19 min

    የመጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም የዜና መጽሔት

    -በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ ለመሻገር ሙከራ ማድረጋቸው የተገለፀ 48 ኤርትራውያንን ማሰሩን የደቡብ ኦሞ ዞን ፖሊስ አስታውቋል። -ጂግጂጋ ውስጥ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ40 በላይ ሱቆች መቃጠላቸውን የሶማሌ ክልል አስታወቀ እነዚህና -በዋግ ህምራ ዞን በእደ ጥበብ ባለሙያዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንዲሁም አዲሱ የዩናይትድ ስቴትስ የቪዛ አሰጣጥ ሕግ

  • March 20 · 21 min

    የመጋቢት 11 ቀን 2018 የዜና መፅሔት

    የዛሬው የዜና መፅሔታችን በዒድ በዓል ላይ ያተኮረ ነው። በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ፣በድሬዳዋ፣በሐዋሳ እና በደሴ የነበረው የበዓሉ ድባብ ያስቃኘናል።

  • March 19 · 25 min

    የሐሙስ መጋቢት 10 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ዜና መጽሔት

    የዜና መጽሔት -በኢትዮጵያ ወቅታዊ ዲፕሎማሲ ላይ የሚሰጡ አስተያየቶች ፣ -በትግራይ ክልል "አፈና እና የዘፈቀደ እሥራት" መኖሩን አንድ የሲቪክ ድርጅት መግለጹ አማርኛ ለምን ከአፍሪካ ህብረት የሥራ ቋንቋዎች አንዱ ሳይሆን ለምን ቀረ? -የነዳጅ ዋጋ ንረት በአሶሳ ፣ እንዲሁም የተወደደው የዒድ ገበያ በደሴ በተሰኙ ርዕሶች ስር የተጠናቀሩ ዘገባዎች ተካተዋል። ሳምንታዊው የባህል መድረክ በኢትዮጵያ የብርሌ ታሪክ ላይ ያተኩራል ።