የዜ

Sunday · 8 min
የሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
በመከላከያ ሠራዊትና በትግራይ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ሸረሪና በተባለ ቦታ የተጀመረው ውጊያ መቆሙን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገበ። እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ፈጸመችው በተባለ የአየር ጥቃት 15 ፍልስጤማውያን ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማስቆም በአፋጣኝ ስምምነት ላይ ከተደረሰ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ላለመሰንዘር መስማማታቸውን ገለጹ። በኢንዶኔዥያ በአንዲት ጀልባ በደረሰ የእሳት አደጋ 5 ተሳፋሪዎች ሞተው 41 የደረሱበት አለመታወቁን የሐገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ።
















