የዓለም ዜና

DW Amharic የሐምሌ 04 ቀን 2018 የዓለም ዜና

July 11 · 10 min · 11.7 MB
0:00-10:38

Streams straight from the publisher. podnod never proxies or re-hosts episode audio.

አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመች። የሱዳን ብሔራዊ ጦር አሜሪካ ያዘጋጀችውን ምክረ-ሐሳብ የሚቀበለው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከተቆጣጠራቸው ከተሞች ለቅቆ ሲወጣ እንደሆነ ቅድመ-ሁኔታ አስቀመጠ። የናይጄሪያ ጦር በዛምፋራ ከ300 በላይ ታጣቂዎች ገደለ ተባለ። የኢራን መንፈሳዊ መሪ ሞሽታባ ኻሜኒ አገራቸው የአባታቸውን ገዳዮች መበቀሏ “አይቀሬ” እንደሆነ ዛቱ። የአሜሪካው ፕሬዝደንት በኢራን ላይ ያነጣጠሩ 1,000 ሚሳይሎች መጠመዳቸውን አስጠንቅቀዋል። ሩሲያ በዩክሬን ላይ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች ስድስት ሰዎች ሲገደሉ 29 ቆሰሉ።