የዓለም ዜና

የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

May 21 · 10 min · 11.2 MB
0:00-10:06

Streams straight from the publisher. podnod never proxies or re-hosts episode audio.

የግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ለመንግሥት አቅርቦት የነበረው ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘቱ በምርጫው ተሳትፎው እጅግ የተቀዛቀዘ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ ።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ቢሮ በክልሉ የ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ከታቀደው አንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚያበቃ አስታወቀ።

ባለፉት 3 ሳምንታት ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፣ ዩጋንዳ ወይም ደቡብ ሱዳን የነበሩ አሜሪካውያን ጠለቅ ላለ ምርመራ ፣በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ብቻ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዲገቡ የአሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሰበ ።